ጌታ ሆይ ተገለጥ
እባክህ ጌታ ሆይ
ስማን እሺ በለን
እሳትህን ጣለው በመካከላችን
በረዶው ሰለቸን ከቦን በዙሪያችን
በግምባር ተደፍተው
በውነት ያመለኩህ
ክብርህን አይተው ነው
የተዋረዱልህ
ስለዚህ ተገለጥ
ተገኝተህ ገላግለን
መሮናል እሳቱ ሰዎች የለኮሱት
ቅንጣትም አልበጀን !
መዝ 85፡6
አቤቱ ትመለሳለህ ታድነንማለህ
ህዝብህም በአንተ ደስ ይላቸዋል
No comments:
Post a Comment